tg-me.com/nibab_lehiwot/155
Last Update:
በመንገዴ ላይ...........
አንድ ቀን ነው አንዲት መልኳ እንኳን እዚህ ግባ የማይባል አይነት ሴት ነች። ድንገት እያለፍኩ ከኋላ ጠራችኝ። ያው እንደተለመደው ስልኬን ከሚጠይቁኝ ብዙ ሴቶች አንዷ ነች ብየ ኩራት በተሞላበት መንፈስ ቀስ ብየ ዘወር አልኩኝ ሳላጋንን በጣም ብዙ ሴቶች የሚወዱት አይነት መልክ፣ ቁመና፣ ስራ እንዲሁም ስብዕና ያለኝ ወጣት ነኝ። ልጅቷ በጣም የተቻኮለች ትመስል ነበር ሰዓት ንገረኝ እባክህ ? ያው እኔን ለማውራት ሰበብ እንደሆነ ገባኝ እና ኮራ ብየ የእጅ ሰዓቴን ተመለከትኩት። 3:00 አልኳት አይኗ ፈጠጠ እዛው በቆምኩበት ጥላኝ ሮጠች። ምን ሆነሽ ነው ብየ እንድከተላት ነው መቼስ ይሄ ሁሉ አይ ሴቶች በቃ መንገድ አያጡም አይደል ብየ በቆምኩበት ፈገግ እንዳልኩ እያየሁ በአይኔ ሸኘኋት።
ሮጠች ሮጠች ልቧ እስኪጠፋ ሮጠች...... አልተከተልኳትም ግን ድካሟ ተሰማኝ የት ነው ምትሮጠው?
ለምን እንደዚህ ደነገጠች? እውነትም እኔን ለመተዋወቅ ብላ ባይሆነስ....... አይ ምን አገባኝ ..... የቆመች መኪናየ ውስጥ ገብቼ ወደስራየ መሄድ ጀመርኩ።
ድንገት ያቺ እንደ ሚዳቋ ስትፈጥን የነበረች ልጅ ተቀምጣ አገኘኋት። እኔን ስታይ ፈጠን ብላ ተነሳችና እጇን እያውለበለበች ፈገግ አለች። መኪናየን አቆምኩ እና አቤት አልኳት እባክህ ሸኘኝ.... .. አረጋገጥኩ በቃ ከእኔ ጋ ለመግባባት ስቃይዋን እያየች ነው። ግን ለወጉ ወደየት ነሽ? አልኳት ወደ ሳሪስ አለች የሚገርመው እኔም መንገዴ ወደዛ ነበር። ከእኔ ጋ ለመግባባት ሳይሆን እኔን "ለመብላት" ነው ሚለት በእነሱ ቋንቋ በማሰቧ ከልቤ አዘንኩላት እና አይ ስራ ረፍዶብኛል ይቅርታ ሌላ ሰው ጠይቂ ብያት መስኮቱን ዘጋሁት። ከዘጋሁት በኋላ የሆነ ነገር እያለችኝ ነበር ግን አልሰማኋትም ወደፊት ነዳሁት።(እንደዚህ አይነት ሴቶች ያናድዱኛል "ጎልድ ዲገር" እንደሚባሉት ያሉ መኪና እና ቤት ያላቸውን ሞኝ ወንዶች የሚያሳድዱ እሷም ከእነሱ መሀል ነች።)
በዋናነት ግን የህክምና ባለሙያ በመሆኔ እሷ በምታወራቸው ወሬወች ራሴን አናድጄ መሄድ አልፈለግኩም ታካሚወቼ ላይ ምንም ተፅእኖ እንዲደርስ አልፈልግም ። ለዛም ነው ከአላስፈላጊ ሰወች እና ወሬወች ራሴን የማርቀው በእጄ የያዝኩት የተከበረውን የሰው ልጅ ህይወት ነውና።
ስራ ገባሁ
አንድ ታካሚ በፍጥነት ኦፕሬሽን መሆን ነበረበት ነገር ግን የሚፈርምለት ቤተሰብ ቶሎ መድረስ አልቻሉም ። ሆስፒታሉ ውስጥ ትልቅ ክርክር ተነሳ ግማሾቻችን ቤተሰቦቹ እስኪመጡ አንጠብቅ አልን። ሆስፒሉ ደግሞ ሃላፊነቱን አልወስድም አለ። በዚህ ተናድጄ ቆየሁ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ሰወቹ ደርሰው ፈረሙ እና ወደ ቀዶ ጥገናው ክፍል ገባን። የአቅማችንን ሁሉ አደረግን ግን ልናተርፈው አልቻልንም።በህይወቴ እንደዚህ የተናደድኩበት እና ያዘንኩት ቀን ትዝ አይለኝም። ተስፋ በቆረጠ አረማመድ እየተራመድኩ ወጣሁ ቅድም ያገኘኋት ልጅ አንገቷን ደፍታ ስቅስቅ ብላ እያለቀሰች አየኋት ።
አይኔን ማመን አልቻልኩም ምን ትሰራለች እዚህ????? አባቷ ናቸው ያረፉት ዶክተር አለች አንዷ ነርስ ከኋላዬ........
ትንፋሽ አጠረኝ በእኔ ምክኒያት ሰው ሞተ? ለታካሚወቼ የምጨነቀው እኔ ራሴ ታካሚወቼን ገደልኳቸው።
ሁሌ ራሴን ትክክል አድርጌ ማሰቤ ትልቅ ስህተት ነበር። ካጋጠሙኝ በጣም ተደጋጋሚ ነገሮች አንፃር ቢሆንም ያደረግኩት ግን ልክ አልነበርኩም። አንዳንዴ ከአንዳንድ ውሳኔወቻችን እና ግምቶቻችን በፊት ቆም ብለን ማሰብ ያስፈልገናል።
ከተቀመጠችበት ሆና አንገቷን ቀና አድርጋ አየችኝ ምናልባት የአባቴ ገዳይ ፣ ጨካኝ፣ አውሬ እያለችኝ ይሆናል በውስጧ) እኔም እየተራመድኩ አንገቴን ሰበር አድርጌ አይቻት
እኔም መንገዴን እሷም ለቅሶዋን ቀጠልን......
ከዚያ ቀን በኋላ በህይወት ዘመኔ አይቻት አላውቅም። ግን አይኗ እስካሁንም ድረስ ይገርፈኛል
መስኮቱን ዘግቼው እያለ ምን ይሆን ያለችኝ ?
@nibab_lehiwot
BY ሕይወትን - በገፅ
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283
Share with your friend now:
tg-me.com/nibab_lehiwot/155